top of page

የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ዋና ጽ/ቤት የ9 ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ በአዲስ አበባ ከተማ እያካሄደ ይገኛል


በመርሀ ግብሩ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት ክቡር አቶ ሞገስ ባልቻ የብልፅግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ ለሁለንተናዊ ብልፅግና ስኬት የማይተካ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ጠቅሰዋል። አያይዘውም ፓርቲው ወጣቶችን በፖለቲካው፣ ኢኮኖሚያዊ፣ እና ማህበራዊ መስኮች በግንባር ቀደምትነት እንዲሳተፉ እና ለውጡንም በባለቤትነት እንዲመሩት በማድረግ ምቹ ሁኔታን መፍጠሩንም ገልፀዋል።

የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት አባንግ ኩመዳን በበኩላቸው የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማስፋት እንዲቻል በወጣት ክንፍ መሪነት ባለፉት 9 ወራት ሰፊ ስራዎች እንደተሰሩ አንስተዋል። በበጀት አመቱ በወጣቶች ክንፍ የተከናወኑ ተግባራት የፓርቲውን ስኬታማ ጉዞ የሚያመላክቱ እና ለታለመው ሁለንተናዊ ስኬትም አቅም እንደሆነም አክለዋል። በአፈፃፀም ግምገማ የተለዩ ጠንካራ ተሞክሮዎችን ለማስቀጠል፣ መልካም ልምዶችን ለመጋራትና ጉድለቶች ለማረም መድረኩ ምቹ ዕድል እንደፈጠረ ተጠቁሟል። የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ዋና ጽ/ቤት ፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ የሆኑት ወጣት ሰብለ በቀለ የጽ/ቤቱን የ9 ወር እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ሪፖርት አቅርብው ውይይት እየተደረገበት ይገኛል፡፡ የግምገማ መድረኩም ለተከታታይ 2 ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።


 
 
 

Comments


bottom of page