top of page

ሃገሬን እገነባለሁ ሃላፊነቴን እወጣለሁ!!


የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወጣቶች ክንፍ "ሃገሬን እገነባለሁ ሃላፊነቴን እወጣለሁ" በሚል መሪ ቃል የደም ልገሳ መርሃ ግብር አካሄደ።

በደም ልገሳዉ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወጣቶች ክንፍ አስተባባሪ የሆኑት ወጣት ያሬድ ተፈራ ዉድ የሆነዉን የሰዉ ሂወት ማዳን የህሊና እርካታን የሚሰጥ ተግባር በመሆኑ ወጣቶች ይሄ በጎ ተግባር በማስተባበርና ደም በመለገስ ለሚያደርጉት አስተዋፆኦ ምስጋናቸዉን አቅርበዋል።

በመርሃ ግብሩም ላይ የብልፅግና የወጣቶች ክንፍ አባላት፣የወረዳ ዘርፍ ሰብሳቢዎች እንዲሁም በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ተሳትፈዋል።

ሚያዝያ 25/2017ዓ.ም


 
 
 

Comments


bottom of page